ታማኝ ልጅ ይሉኃል መምህር አስታራቂ
የተዋሕዶ ልጅ የበጎች ጠባቂ
ተኩላ አይቶ የማይሸሽ ማተቡን አጥባቂ
ጥሪህን ተመልከት እንዳትዘናጋ
ቤተ ክርስቲያንህን ለማገልገል ትጋ
ነገር ግን ተጠንቀቅ
ከሰው አትጠብቅ የድካምህን ዋጋ
የወንጌል አዝማራ ስፋቱ ይደንቃል
ጽጌው ፍሬ ሲይዝ ለሁሉም ይበቃል
ይታይሃል ከሩቅ የተዋሕዶ አዝመራ
እሸቱ ያማረ ፍሬው የጎመራ
ይጠበቅብሃል ገና ብዙ ሥራ
ታጥቀህ ድረስለት ውጣ ተሠማራ
የኋላህን ሰብስብ የፊትህን ዝራ
ለወንጌል ተልዕኮ ታማኝ ሁን አደራ
ጉዞ ጀምረሃል በአባቶችህ መንገድ
ግራ ቀኝ እያየህ በጥንቃቄ ሄድ
በመንፈሳዊ ጎዞ በወንጌል ጎዳና
ቃል ሕይወት ይሁን ሥራህ ደማቅ ፋና
ዳሩ መሰናክል አይታጣምና
ሥራህን አከናውን በፍቅር በትህትና
በጣም ዝቅ አትበል እውቀት እንዳነሰው
ይህ ዓለም አይወድም እንዲህ ዓይነቱን ሰው
በጣምም ከፍ አትበል ጣራ እንዳትነካ
This is America
ዱሮም የሰው ምክር ሁል ጊዜም አይሠራ
አንደኛው ወደ ቀኝ ሌላው ወደ ግራ
በኅሊናህ ፋባ በራስህ ተመራ
ሁሌም ለወንጌል ቃል ታማኝ ሁን አደራ